Quantcast
Channel: The Habesha: Latest Ethiopian News, Analysis and Articles
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13041

የፀጥታው ምክር ቤት መንግስት በትግራይ ያደረገውን የተናጥል የተኩስ አቁም አደነቀ

$
0
0

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ያደረገውን የተናጥል የተኩስ አቁም አደነቀ፡፡

ምክር ቤቱ በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ስብሰባ ያደረገ ሲሆን፥ በስብሰባው ወቅትም በመንግስት የተወሰደውን የተኩስ አቁም በማድነቅ እርምጃው በክልሉ ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት ከማገዝ አንጻር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል፡፡

ዘላቂ ሰላም ከማምጣት አንጻርም ሁሉንም አካላት ያሳተፈ ሃገር አቀፍ ውይይት ሊደረግ ይገባልም ነው ያለው፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት እንዲደግፍና እንዲያበረታታም ምክር ቤቱ ጠይቋል፡፡

ከሰብአዊ ድጋፍ ጋር ተያይዞም ረጂ ድርጅቶች በክልሉ የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያሳድጉም ነው ምክር ቤቱ የጠየቀው፡፡

ከዚህ ባለፈም የተከዜ ድልድይ መፍረሱን ተከትሎ መንግስት ለሰብአዊ ድጋፍ የአውሮፕላን በረራ መፍቀዱንም አድንቋል፡፡

በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በዚህ ወቅትም በመንግስት በኩል እየተሰሩ ያለ ስራዎች ሊበረታቱ እና እውቅና ሊሰጣቸው እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

አያይዘውም የተኩስ አቁሙ በክልሉ የሚደረገውን ሰብአዊ ድጋፍ ለማሳደግ እንዲረዳ ታስቦ የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰው፥ ሁሉን ያሳተፈ ውይይት ለማድረግ እድል እንደሚሰጥም አስረድተረዋል፡፡

ከሰብአዊ ድጋፍ አንጻርም መንግስት ከረጂ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከሰብአዊ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘም በጉዳዩ ላይ የተሳተፉ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡

አምባሳደር ታዬ በንግግራቸው በኢትዮጵያ ላይ አላግባብ እየተደረጉ ያሉና የሚደረጉ ጫናዎች ሊቆሙ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!



Source link

The post የፀጥታው ምክር ቤት መንግስት በትግራይ ያደረገውን የተናጥል የተኩስ አቁም አደነቀ first appeared on Satenaw Ethiopian News/Breaking News.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13041

Trending Articles